መዝሙር (የሰው ልጅ ሁልጊዜ) March 7, 2021 (First Mezmur)

  • Print
የሰው ልጅ ሁልጊዜ በጣም ደስ ቢለው በጣም ደስ ቢለው /፪/
ደግሞ የጭንቁን ቀን ማሰብ ተገቢ ነው /፪/
ምንም ቢደሰቱ ቢበዛ ምቾት ቢበዛ ምቾት /፪/
አይቀርም በዃላ መወሰድ በሞት /፪/
ችግር ቢደራረብ ሃዘን ቢከበን ሃዘን ቢከበን /፪/
ከክርስቶስ ፍቅር ማንም አይለየን /፪/
ሳናውቀው ዲያቢሎስ እንዳይነጣጥለን እንዳይነጣጥለን /፪/
ነቅተን እንጠብቅ የእምነት ሰይፍን ይዘን /፪/