የተሐድሶ መናፍቃን ድፍረት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ለመቀልበስ እስከ መሞከር

የተሐድሶ መናፍቃን ድፍረት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ለመቀልበስ እስከ መሞከር አትም ኢሜይል

ባለፉት ተከታታይ ዕትሞች ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ስልትና ግብ ማቅረባ ችን ይታወቃል፡፡ በዚህ ዕትም ደግሞ ተሐድሶ መናፍቃን ጥፋታቸውን አምነ ውና ተጸጽተው ከመመለስ ይልቅ የቅ ዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ካለመቀበል አልፎ ውሳኔዎችን ለማስቀልበስ እስከ መሞከር ድረስ የሚያደርጉትን ከንቱ ሩጫ እናቀር ባለን፡፡ መልካም ንባብ!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ ብዙ ፈተና ዎችን እንዳሳለፈችና ፈተናዎቹ መልካ ቸውን እየለዋወጡ ራሳቸውን የሚደ ግሙ እንጂ አዲሶች እንዳልሆኑ ባለፉት ጽሑፎች ተመልክተናል፡፡ በዚህ ክፍለ ዘመን ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ፈተና የሆኑት ተሐድሶ መናፍቃን አስተም ህሯቸውና ዓላማቸው ፕሮቴስታንታዊ ሆኖ ሳለ ኦርቶዶክሳዊ ነን በማለት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብተው ብዙ የዋሀ ንን ከበረታቸው ለማስወጣት እየሠሩ ነው፡፡ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ በዋናነት የቤተ ክርስቲያን ምንጮችን በመለየት፣ ምንጮቹ ውስጥ ሠርጎ በመ ግባት፣ አስተምህሮ በመቀየርና የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር በመቆጣጠር ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ለመረከብ፣ መረከብ ካልቻሉ ደግሞ እንደ ሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው፡፡ በተሐድሶ መናፍቃን የቤተ ክርስቲያን የእምነትና የመንፈሳዊነት ምንጮች ተብለው ለጥፋት ተልእኳቸው ዒላማ የተለዩት ደግሞ የአብነት ትምህርት ቤቶች (የሊቃው ንተ ቤተ ክርስቲያን መፍለቂያ ስለሆኑ)፣ ገዳማት (የሊቀ ጳጳሳትና ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት መፍለቂያዎች ስለሆኑ)፣ መንፈሳዊ ኮሌጆች (የስብከተ ወንጌል ሓላፊ ዎችና የመምህራን መፍለቂያዎች ስለ ሆኑ)፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች (ወጣቶ ችንና ምእመናንን ለማግኘት የተመቹ መድረኮች ናቸው ብለው ስላሰቡ) እና የቤተ ክርስቲያን መዋቅር (ድጋፍና ሽፋን ለማግኘት ይጠቅመናል ብለው ስላሰቡ) ናቸው፡፡
ቤተ ክርስቲያንም የተሐድሶ መና ፍቃንን እንቅስቃሴ ለመግታት በተለያዩ ጊዜያት ተኩላዎችን ከበጎች የመለየት ሥራ ሠርታለች፡፡ በተለይም ምእመናንን የመጠበቅ ሓላፊነት ያለበት ቅዱስ ሲኖ ዶስ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጋቸው ጉባ ኤያት ላይ የተሐድሶ መናፍቃንን መሰሪ አካሔድ ተረድተን እንድንጠነቀቅ ያላሳሰ በበት ጊዜ የለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ ቅዱ ሳን ሐዋርያት በአመክንዮአቸው “እኛስ የሃይማኖት ለዋጮችን ግብር እንጸለየ ፋለን” ብለው ባስቀመጡት መመሪያ መሠረት የተሐድሶ መናፍቃንን ኑፋቄ ነቅሶ በማውጣትና የሃይማኖት ለዋጭ ነት ግብራቸውን በማውገዝ መመለስ የፈለጉትን ተመክረው፣ ቀኖና ተሰ ጥቷቸው፣ መምህራን ተመድበውላ ቸው እንዲማሩና ወደ ቤተ ክርስቲ ያን አንድነት እንዲጨመሩ፤ ቀኖናውን ለመቀበልና ለመማር ፈቃደኛ አንሆንም፣ ርትዕት ወደሆነችው ሃይማኖትም አንመለስም ያሉትን ደግሞ ከቤተ ክር ስቲያን አንድነት እንዲለዩ አድርጓል፡፡ በተለይም በ፲፱፻፺ ዓ.ም እና በ፳፻ወ፬ ዓ.ም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮን የሚጠብቁ ሳይሆኑ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ነን በማለት ሲያደናግሩ የነበሩ ተሐድሶ መናፍቃን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘዋል፡፡ የተሐድሶ መናፍቃን አቀንቃኞችን በማውገዝ ብቻ እንቅስቃሴውን መግታት እንደማይቻል የተረዳው ቅዱስ ሲኖዶስ የተሐድሶ መናፍ ቃን ምንጫቸው ምንድን ነው የሚለ ውን ለማወቅ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ባለሙያዎችን ያካተተ ሁሉን አቀፍ የሆነ ጥናት አጥንቶ የሚያቀርብ ኮሚቴ ሠይሞ ቅዱስ ሲኖዶስ በበላይ ነት እየመራና መመሪያ እየሰጠ ጉዳዩ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ክትትል እያደረገ ነው፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በተለይም ከ፳፻ወ፬ ዓ.ም ጀምሮ የተሐድሶ መናፍቃንን ጉዳይ ዋና አጀንዳ አድርጎ በየጉባኤው ሲወያ ይበት እንደነበር የቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤያት ያሳያሉ፡፡ ጉባኤው በመደበኛ ጉባኤያቱ ላይ ተሐድሶ መናፍቃን በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠርገው በመግባት ጥፋት እያደረሱ እንደሆነና እንቅስቃሴው በሁሉም አህጉረ ስብከት የሚታይ መሆኑን አስቀምጧል፡፡ በዚህ መነሻነት የተሐድሶ መናፍቃን መገኛ ምንጫቸው ከየት እንደሆነ ለመለየት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡ በውይይቱም ተሐድሶ መናፍቃን ሠርገው በመግባት ብዙ ጥፋት እያደረሱባቸውና ኦርቶዶክሳ ውያን ልጆችን መናፍቅ ለማድረግ ትኩ ረት አድርገው ከሚሠሩባቸው የቤተ ክርስቲያን ተቋማት መካከል መንፈሳዊ ኮሌጆቻችንም የሚገኙበት በመሆናቸው በእነዚህ የቤተ ክርስቲያን የትምህ ርት ተቋማት ላይ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ በማለት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ስለዚህም የመንፈሳዊ ኮሌጆች የተማሪ አቀባበል፣ የትምህርት አሰጣጥ፣ የመም ህራን ማንነትና ምንነት እንዲሁም የማስተማሪያ መጻሕፍት ሊፈተሹና ሊመረመሩ እንደሚገባቸው በመግለጽ ጉዳዩን በጥልቀት አጥንቶ የሚያቀርብ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሠራ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ጉዳዮችን አስቀድሞ በማየትና ብፁዓን አባቶች በየአህጉረ ስብከታቸው እየተካሔዱ ያሉ እንቅስቃሴዎችን መነሻ በማድረግ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ውሳኔዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ከምእመናን የሚ መጡ ጥቆማዎች በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ለሚሰጣቸው ውሳኔዎች ትልቅ ግብዓት ሆነው አገልግለዋል፡፡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም በየአህጉረ ስብከታቸው እንዲሁ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ እር ምጃዎችን ለመውሰድ በራሳቸው ክት ትል ከሚደርሱባቸው እውነታዎች በተ ጨማሪ ከሕዝበ ክርስቲያኑ የሚመጡ ጥቆማዎችን በግብዓትነት ይጠቀማሉ፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን ከጊዜ ወደ ጊዜ ሥውር ዓላማቸውን ዕውን ለማድረግ በቤተ ክርስቲያን ላይ እያካሔዱት ያለው የጥፋት እንቅስቃሴ በሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ እየታወቀ መጥቷል ብለን እናምናለን፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በተሐ ድሶ መናፍቃን ላይ በየጊዜው የሰጣቸው ውሳኔዎች ምእመናን ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ከማድረጉም በላይ እንቅስቃሴ ውን ለመግታት የራሳቸውን ሓላፊነት እንዲወጡም አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ያለው ግንዛቤና በእንቅስቃሴው አደገኛነት ላይ ያለው መረዳት ማደጉ በጉዳዩ ላይ ያገባኛል የሚል ስሜት እንዲ ያሳድር አድርጓል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስና የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ውሳኔዎች ያበረ ታቷቸው ምእመናን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ እየተ ካሔደ ያለውን የውስጥም ሆነ የውጪ ሴራ የማክሸፍ እንቅስቃሴን የራሳቸው ጉዳይ አድርገው እንዲሠሩ እገዛ አድር ጎላቸዋል፡፡ የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስ ቃሴ ሥውር ዓላማና ቤተ ክርስቲያ ንን የማፍረስ ተልእኮ ጠንቅቀው የተረዱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ማኅበራት፣ ምእመናን እና ወጣቶች መረጃዎችን ስለ እንቅስቃሴው በቂ ግንዛቤ ለሌላ ቸው ምእመናን ለማዳረስ ያደረጉት ጥረት ከፍተኛ ነው፡፡ እነዚህ አካላት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መከታተላቸው እና መረጃው የሌላቸውን ምእመናን ለማንቃት ሰፊ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው የተሐድሶ መናፍቃንን መሰሪ ተግባር በማጋለጥ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን በየቦታው የሚያ ደርጉትን ሥውር እንቅስቃሴ በማጋ ለጥ፣ መረጃዎችን በማሰባሰብ ለሚመለ ከታቸው አካላት በማቅረብ፣ ስለ እንቅስ ቃሴው አደገኛነት ግንዛቤ መፍጠሪያ መርሐ ግብራትን በማዘጋጀት እውነቱ ከሐሰቱ እንዲለይ በማድረግ ትልቅ ሥራ ሠርተዋል፡፡ ግንዛቤ መፍጠሪያ መርሐ ግብራቱ አብዛኛው ምእመናን የቤተ ክርስቲያንን መምህራን የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡ ነጣቂ ተኩላዎች ለይ ተው እንዲያውቁ አድርገዋል፡፡ በዚህ መነሻነት ብዙ ምእመናን የተሐድሶ መና ፍቃንን ሥውር ሴራ በመገንዘብ በግ ልም በማኅበርም በመደራጀት እንቅስቃ ሴውን ለመግታት እየተጉ ይገኛሉ፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በተለያዩ ጊዜያት የሰጣቸውን ውሳኔዎች እና አቅጣጫ ዎች መሠረት በማድረግ ብዙ አህጉረ ስብከት የተሐድሶ መናፍቃንን ዓላማ አንግበው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠርገው በመግባት ምእመንን የሚያደናግሩ ክፉዎች ሠራተኞችን ከአገልግሎታቸው አግደዋል፡፡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በየአህጉረ ስብከታቸው ለተሐድሶ ዓላማ አስፈጻሚ የሆኑት ልብ ገዝተው መመለስ ለሚፈልጉት ቀኖና በመስጠት እንዲታረሙ፣ ለመመ ለስ ፈቃደኛ ላልሆኑት ደግሞ ተወግ ዘው እንዲለዩ በማድረግ የኖላዊነት ሓላፊነታቸውን በመወጣት አርአያና ተጠቃሽ የሚሆን ተግባር አከናውነ ዋል፡፡ ምእመናንን ከሐሰተኞች መምህ ራን የመጠበቅ ሓላፊነት ያለባቸው ብፁ ዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የየሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች በተለይም ከ፳፻ወ፬ ዓ.ም ወዲህ በአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤያት ላይ በዚህ ዘርፍ የተሠሩ ሥራዎችን በሪፖርታቸው ያላቀረቡ በት አጋጣሚ የለም፡፡ በሪፖርታቸው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሠር ገው በመግባት የቤተ ክርስቲያንን እን ጀራ እየበሉ የሉተርን ዓላማ ለማስፈ ጸም የሚሠሩ ተሐድሶ መናፍቃንን በማ ጋለጥና አንዳንዶችንም ከአገልግሎት በማገድ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን መፈ ጸም መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡ ሪፖርቱ በሚቀርብበት ወቅት ከተሰብሳቢዎች ይቀርብ የነበረው ድጋፍ የሚያሳየው ተሐድሶ መናፍቃን በሁሉም ቦታ የሚያ ካሒዱት ቅሰጣ ምን ያህል የሚያሳምም እንደሆነ እና እንቅስቃሴውን ለመግታት የሚሠሩ ሥራዎች ደግሞ በተሰብሳቢ ዎች ዘንድ ምን ያህል ተስፋ ሰጪ ዎችና አስደሳቾች እንደሆኑ ማሳያ ነው፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ኮሌጆችን የከፈተችው ሐዋርያዊ አገልግ ሎቷ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ ነው፡፡ በእነዚህ መንፈሳዊ ኮሌጆች ተም ረው እስከ ጵጵስና መዓርግ ደርሰው ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የነበሩ፣ በማገልግል ላይ የሚገኙ አባቶች አሉ፡፡ ዛሬም ቢሆን በመናፍቃን ስውር ዘመቻ ከአማናዊቷ እምነት ፈቀቅ ያሉና በኑፋ ቄያቸው ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የተለዩ አንዳንድ ግለሰቦች እና ጥቂት ደቀ መዛሙርት ቢኖሩም በርትዕት ሃይ ማኖት ጸንተው የተሐድሶን ስውር ደባ ሲታገሉ የነበሩና እየታገሉ የሚገኙ ጽኑዐን ደቀ መዛሙርት በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ መኖራቸው ልብ ሊባል ይገባል፡፡ ተሐድሶ መናፍቃኑ መንፈሳዊ ኮሌጆችን “የእኛ ዓላማ ማስፈጸሚያ ናቸው”፤ ከመንፈሳዊ ኮሌጆች ተመርቀው የሚወጡ ደቀ መዛሙርትን ደግሞ “በሙሉ ልባችን እንቀበላቸዋለን”፣ ወዘተ በማለት እነዚህን የቤተ ክርስቲያ ናችንን ተቋማት ምእመናን እንዲጠራጠ ሯቸውና እንዲሸሿቸው፣ ከፍሬያቸውም በንጹሕ ልብ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የሚቻላቸውን ሁሉ ሲሠሩ እደኖሩ ይታወቃል፡፡ ተሐድሶ መናፍቃን ይህን እኩይ ተግባር ቢፈጽሙም መንፈሳዊ ኮሌጆች አሁንም የብዙ ሰባክያነ ወንጌል መፍለቂያዎች፣ የብዙ እውነተኛ መም ህራን መገኛዎች መሆናቸውን መረዳት ይገባል፡፡ ስለዚህ ምእመናንም ሁሉንም በጅምላ ከመጠራጠር ርቀን በፍሬያ ቸው ታውቋቸዋላችሁ እንደተባለ በትም ህርታቸው መለየት ይኖርብናል፡፡ ሁሉ ንም በጅምላ መጥላት ከጀመርን ግን ሳናውቀው የተሐድሶ መናፍቃንን ዓላማ እያስፈጸምንላቸው መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው፡፡
ሆኖም ግን በእነዚህ ኮሌጆች ውስጥ ኦርቶዶክሳውያን መስለው ገብተው ብዙ ጥፋት እያደረሱ ያሉ፣ መንፈ ሳዊ ኮሌጆች ውስጥ ተምረው ያለ ፉና በመማር ላይ ያሉ ኑፋቄ ያለባ ቸው ደቀ መዛሙርት እንዳሉ በተለያዩ ጊዜያት መናፍቅነታቸው ታውቆ ከመን ፈሳዊ ኮሌጆች የተባረሩና በቅዱስ ሲኖ ዶስ ምልዐተ ጉባኤም ተወግዘው የተ ለዩ ግለሰቦች ማስረጃዎች ናቸው፡፡ በመ ንፈሳዊ ኮሌጆቹ ውስጥ የመናፍቃን ተላላኪዎች መሆናቸው የተረጋገጠባ ቸው ተማሪዎች ከመንፈሳዊ ኮሌጆች ሲባረሩ ጉዳዩን ፖለቲካዊ መልክ በመስ ጠት ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመ ለስ ቢሞክሩም የየተቋሞቹ የቦርድ አመራሮች እስከ መጨረሻ ድረስ በመከ ታተል ውሳኔው እንዲጸና በማድረግ አኩሪ ተግባር ፈጽመዋል፡፡ ይህም ሊደ ገፍ፣ ሊበረታታና በአርአያነት ሊጠቀስ የሚገባው ተግባር ነው፡፡ ተሐድሶ መናፍ ቃን በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ ሊሠ ሩት ያቀዱትን ሴራ በማክሸፍ በኩል ከተሐድሶ መናፍቃን ጋር አንገት ለአን ገት ተናንቀው መረጃ በማሰባሰብ አደራ ጅተው ለየኮሌጆቹ አስተዳዳር በማቅረብ መንፈሳዊ ኮሌጆችን ከሠርጎ ገቦች ለመጠበቅ በአርአያነት የሚጠቀስ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙ ደቀ መዛሙርት አሉ፡፡ እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ልጆች መንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ የራሳቸውን ሥውር ዓላማ ለማሳካት የሚሠሩ ተሐ ድሶ መናፍቃንን በማጋለጥና ተገቢው ውሳኔ እንዲሰጣቸው ለማድረግ መረጃ ዎችን ከማሰባሰብ ጀምሮ ያደረጉት ተጋ ድሎ በጊዜው የሚገኝ ጥቅምን ንቆ ዘለዓ ለማዊ ርስትን በመናፈቅ ከመናፍቃን ጋር ብዙ ተጋድሎዎችን ፈጽመው ያለፉ ቅዱሳን አበውን አርአያነት የተከተለ ነው፡፡ መንፈሳዊ ኮሌጆችን የሚመሩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የተቋማቱ ሓላ ፊዎችም በኦርቶዶክሳዊ ተማሪዎች መካከል በተሐድሶ መናፍቃን አቀነባባ ሪነት ሠርገው የገቡ መናፍቃንን ለመለ የት በየጊዜው ብዙ ሥራዎችን ሠርተ ዋል፡፡ የመንፈሳዊ ኮሌጆች ቦርዶችም በተለያዩ ጊዜያት የመናፍቃን ዓላማ አስፈጻሚ የሆኑ ግለሰቦች ላይ የቀረቡ መረጃዎችን መርምረው ኑፋቄያቸው በመረጃ የተረጋገጠባቸውን ከመንፈሳዊ ኮሌጆች እንዲባረሩ አድርገዋል፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን እስካሁን ድረስ “ኦርቶዶክሳውያን ነን”፣ “የጥንታዊ አባቶች ልጆች ነን”፣ “ቤተ ክርስቲያንን ወደ ጥንታዊ አስተምህሮዋ እንመልሳ ለን”፣ ወዘተ የሚሉ የማደናገሪያ ቃላ ትን በመደርደር የዋሀንን ሲያታልሉ ቆይተዋል፤ አሁንም በማታለል ላይ ናቸው፡፡ “ወደ እግዚአብሔር መሔጃ መንገዱ ብዙ እንጂ አንድ ብቻ አይደ ለም”፣ “ሁላችንም የምናመልከው የተሰ ቀለውን አንድ ኢየሱስ ነው”፣ ወዘተ በማለት በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በፕሮቴስታንት መካከል የአስተምህሮ ልዩነት የሌለ ለማስመሰል ብዙ ጥረዋል፡፡ ቅድስትና ሐዋርያዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋ ሕዶ ቤተ ክርስቲያንም እነዚህ አካላት “ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን” በሚል ሰበብ የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ሥርዓት እና ትውፊት በመቀየር ወይም በመቀየጥ ፕሮቴስታንታዊ ለማድ ረግ የሚሠሩ መሆናቸውን በመግለጽ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አሳውቃለች፤ እያሳ ወቀችም ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን አስ ተምህሮ ለመቀየር ደፋ ቀና ሲሉ የነ በሩ ተሐድሶ መናፍቃን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲ ያን አንድነት የተለዩ ቢሆንም አሁንም ራሳቸውን ቀሲስ፣ መምህር፣ ዲያቆን፣ ወዘተ እያሉ በመጥራት ስለሚያደናግሩና ከአንዱ ቦታ ሲነቃባቸው ወደ ሌላ ቦታ በመሔድ ስውር ተልእኳቸውን እየፈ ጸሙ ስለሆነ ቅዱስ ሶኖዶስ ከውሳኔው በተጨማሪ አፈጻጸሙን ሊያጤነው ይገ ባል እንላለን፡፡
የሁሉም አካላት መተባበር ዓላማ ቸውን እንደሚያከሽፍባቸው የተረዱት ተሐድሶ መናፍቃን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰ ጣቸውን ውሳኔዎች የማጣጣልና ቤተ ክርስቲያንን የማቃለል ሥራዎችን ለዚሁ ዓላማ ማስፈጸሚያ በከፈቷቸው ድረ ገጾች ሲያስተጋቡት እንደቆዩ በሁሉም ዘንድ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህ ደግሞ አቅ ጣጫ በማስቀየርና በማዘናጋት የፈለጉ ትን ጉዳይ ለመፈጸምና ለማስፈጸም የሚጠቀሙበት ስልት ነው፡፡ እነዚህ አካላት መናፍቅነታቸው ተረጋግጦ ተወ ግዘው ከቤተ ክርስቲያን መለየታቸው፣ ከአገልግሎት መታገዳቸው እና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሴራቸው መገለጡ ተሳስተ ናል እንመለስ እንዲሉ አላደረጋቸውም፡፡ ይህን በማለት ፋንታ በተለያዩ ድረ ገጾቻ ቸው ላይ ውሳኔውን በሰጠው በቅዱስ ሲኖዶስ ሲሳለቁና ቤተ ክርስቲያንን ሲሳደቡ ቆይተዋል፡፡ በድርጊታቸው አፍ ረው ከመመለስና ከመጸጸት ይልቅ ቤተ ክርስቲያንና ቅዱስ ሲኖዶስን በማቃለል ምእመናን በብፁዓን አባቶች ላይ ያላ ቸው እምነት እንዲጠፋና ጥርጣሬ እንዲ ያድርባቸው ማድረግን እንደ ሥራ ተያ ይዘውታል፡፡ ይህ ድርጊታቸው ተሐ ድሶ መናፍቃን ምን ያህል ክፉ መንፈስ እንደተቆጣጠራቸውና እግዚአብሔርን እንደ አምላክነቱ ስላላከበሩት ለማይገባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው የሚለው የመጽሐፍ ቃል እየተፈጸመባቸው እን ደሆነ ማሳያ ነው፡፡ የድፍረታቸው ድፍ ረት በአሁኑ ወቅት ቤተ ክርስቲያንን የሚመራት መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ግለሰ ቦች ናቸው በማለት ምእመናንን ከቤተ ክርስቲያን ለማስወጣትና የቅዱስ ሲኖ ዶስን ውሳኔ እንዳይቀበሉ ለማድረግ ብዙ ብለዋል፡፡ በተለይም አባ ሰላማ፣ ጮራና ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የሚባሉት ድረ ገጾቻቸው ቅዱስ ሲኖ ዶስ ያወገዛቸውን ተሐድሶ መናፍቃንን በመደገፍና ቅዱስ ሲኖዶስንና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በማቃለል ድፍረት የተሞሉ ጽሑፎችን የሚያወጡባቸው የስድብ አፎቻቸው ናቸው፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን በ፳፻ወ፬ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተላለፈ ውን ውሳኔ ተከትለተው አባ ሰላማ በሚ ባል ድረ ገጻቸው ላይ “ተወጋዦች አው ጋዦች፣ አውጋዦች ተወጋዦች የሆኑ ባት ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርእስ ባወ ጡት ጽሑፍ ላይ ቤተ ክርስቲያንን እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን እንዲህ በማ ለት ነበር የተሳደቡት፡-
ባለፉት ፳ ዓመታት ተወግዘው የተ ባረሩ ሁሉ በሕጋዊ አካል ተወግዘው የተባረሩ አይደሉም። በሕገ ወጦችና በማያስወግዝ ምክንያት በሕገ ወጥ መንገድ «የተወገዙ» ናቸው። የሕግ የበላይነት ባልሰፈነባትና ሁሉም አዛዥ በሆነባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መወገዝ የሚገባቸው ሰዎች መወገዝ የማይገባቸ ውን ሰዎች ሲያወግዙ ኖረዋል። ይኸው አሠራር አሁንም ቀጥሏል። ቤተ ክር ስቲያኗ ምን ያህል እንደዘቀጠች፣ ምን ያህል አንቱ የሚባል ሰው እንደታጣ ባት፣ ምን ያህል ከክርስቶስና ከሐዋር ያት፣ እንዲሁም ከሠለስቱ ምእት ትምህርት እንደራቀች ያሳያል።
“በረከታችሁም ሆነ ውግዘታችሁ ማንንም አያድንም፣ አይገድልምም” በሚል ርእስ በጻፉት ሌላኛው ጽሑፋ ቸው ደግሞ ከሐዋርያት ጀምሮ ባልተቋረጠ ሐዋርያዊ ክትትል ሥልጣነ ክህ ነት ያላቸውን ሊቃነ ጳጳሳት በማቃ ለልና ከተሐድሶ መናፍቃን በማሳነስ፡-
አንድ መንፈሳዊ ሥልጣን የሌለ ውና ለመንፈሳዊ ሥልጣንም የማይገዛ ስመ መንፈሳዊ የመናፍስትና የሙታን ጠሪ ስብስብ አንድ መንፈሳዊ የወን ጌል አገልጋይ የማውገዝም ሆነ የመለ የት ሥልጣን የለውም። አቅም ያንሰዋል! ኃይል ያለው ሥራ ለመሥራት በጥቂ ቱም ቢሆን ኃይል ያስፈልጋል። ይህ ማለት በሌላ አገላለጽ ሥጋ የሥጋን ሥራ ከመሥራት በዘለለ በመንፈሳዊ ዓለም ላይ አሁንም በድጋሜ እጽፈዋለሁ አንዳች ሥልጣን የለውም።
በማለት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንደማይገዙ ብቻ ሳይሆን ቅዱስ ሲኖ ዶስ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን ያለው አካል እንዳልሆነ አድርገው ጽፈዋል፡፡ በዚሁ ለጥፋት ዓላማ በከፈቱት አባ ሰላማ በሚባለው ድረ ገጻቸው ቋሚ ቅዱስ ሲኖዶሱ በ፳፻ወ፯ ዓ.ም በተሐድሶ መናፍቃን ላይ የወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ “ክርስቶስን የምታሳድድ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ቤተ ክርስቲያን ትሆና ለች?” በሚል ርእስ “ሲኖዶሱ በአንድ በኩል ፍልሰት በዝቶአል እያለ ሲናገር በሌላ በኩል ደግሞ ወንጌል እየሰበኩና ሕዝቡን ከፍልሰት እየገቱ ያሉ አገልጋዮ ችን ማሳደድ ሥራየ ተብሎ ተይዟል” በማለት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ አጣጥ ለውታል፡፡
ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በሚለው ድረ ገጻቸው ደግሞ ቅዱስ ሲኖዶስ ከሐዋርያት እውነት የራቀ ለቅዱሳን የጸጋ ስግደት ይገባል ብላ የምታስተምር ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን መና ፍቅ፣ ራሳቸውን ደግሞ ጻድቃን አድር ገው ቅዱስ ሲኖዶስም ቅዱሳን የሆኑ እነርሱን እያሳደደ መናፍቅ የተባሉ ኦርቶ ዶክሶችን እንደሚደግፍ በዚህ መልክ አቅርበዋል፡፡
ሲኖዶሳችን እውነትን እንደ ሐዋርያት ቢያውቅና ቢከተል ኖሮ እነዚህን ለማርያም፣ ለመስቀል፣ ለታቦት፣ ለሥ ዕል [የጸጋ ስግደት] መስገድ አይገባም ብለው የሚሟገቱ ሰዎችን ስም በማክ ፋት መናፍቅና ጸረ-ማርያም ብለው በሥ ቃይ እንዲሞቱ ያደረጉ ጸረ-ኦርቶዶክስ አቋም ይዘው ዘወትር በኦርቶዶክስ ተዋ ሕዶ ጥላ ሥር የሚነግዱ መናፍቃንን እሺ ቢሉ በትምህርት ይመልስልን፣ እንቢ ቢሉ ደግሞ በውግዘት ይለይልን ነበር፡፡ እንደ አለመታደል ሆኖ ሲኖዶሳ ችን መናፍቃንን በመደገፍ ጻድቃንን ያሳድዳል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምት ፳፻ወ፯ ዓ.ም መደበኛ ጉባኤው ላይ ስለ ተሐድሶ መናፍቃን በተያዘው አጀንዳ ላይ በተ ወያየበት ወቅት ከችግሩ አሳሳቢነት አንጻር ኮሚቴ ተቋቁሞ ሰፋ ያለ ጊዜ ተሰጥቶት ጥናቱን በጥልቀት አጥንቶ እንዲያቀርብ በወሰነበት ወቅት “ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶን ከመቀበል ይልቅ ለማጥናት ኮሚቴ የማቋቋሟ አንድምታ” በሚል ጽሑፍ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያሰቡት ዓላማቸው እንዳይከሽፍባቸው ቅዱስ ሲኖዶስን በመቃወም እንዲህ ጽፈዋል፡፡
ከታሪክ መማር የተሳነው ቅዱስ የተባለው ሲኖዶስ ለአስፈላጊውና ለጠቃ ሚው የተሐድሶ እንቅስቃሴ ሌላ ስም በመስጠትና በቤተ ክርስቲያን ሌላ ትልቅ አደጋ ጋርጧል በሚል በማኅ በረ ቅዱሳን ከሳሽነት ሕጋዊም፣ መንፈ ሳዊም፣ ሞራላዊም፣ ሕሊናዊም አካሔድን ባልተከተለና ግብታዊነት በተሞላው መንገድ ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ውግዘት አስተላለፈ፡፡ … በዚህ ዘመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስ ቲያንንና ሃይማኖትን ከተሐድሶ አራማ ጆች ትምህርት ለመጠበቅ በሚል ተሐ ድሶ ሲል የፈረጃቸውን ወገኖች በማሳ ደድና በማውገዝ ተግባሩ ገፍቶበታል፡፡ ስለተሐድሶ እንዲያጠኑ በሚል ሰዎች ንም ጠቅላይ ቤተክህነት መድቧል፡፡ ጥናቱ አስፈላጊ ሊሆን ቢችልም ትኩ ረቱ ግን ተሐድሶን ለማጥፋት የሚል መሆኑ ቤተክህነቱ አሁንም በእንቅልፍ ላይ እንደሚገኝ የሚያሳይ ነው፤
በ፳፻ወ፬ ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ከተወገዙት ግለሰቦች መካከል አሸናፊ መኮንን፣ አግዛቸው ተፈራና ጽጌ ሥጦ ታው ውግዘቱን በመቃወም ስላስገቡት “የይግባኝ ደብዳቤ” ሲያትቱ ደግሞ፡-
የግንቦቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ቤተ ክርስ ቲያንን የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ በማድረግ ያዋረደበትን ውሳኔ ማሳ ለፉ ይታወሳል፡፡ ይህን የራሱን ክብር የቀነስበትን፣ በታሪክ ተወቃሽ የሚያደ ርገውንና ብዙዎችን ያሳዘነውን፣ የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ባልተከ ተለና፣ በየትኛውም መስፈርት ሲመዘን ሕገ ወጥ ሆኖ የተገኘውን ውግዘት፣ «ተወጋዦቹ» እየተቃወሙት ነው፤ በማለት ጽፈዋል፡፡
ውሳኔውን የተሳሳተና ሕገ ወጥ በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስም ቤተ ክርስ ቲያንን የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ እንድትሆን ያደረጋት አስመስለው ጽፈ ዋል፡፡ በእርግጥ ይግባኝ አቅራቢ የተባ ሉት ተወጋዦችም ያስገቡት ደብዳቤ በአባ ሰላማ ድረ ገጽ እንደወጣው ይቅ ርታ ይደረግልን ወይም ተሳስተናልና እንታረም የሚል ሳይሆን በጽጌ ሥጦ ታው አገላለጽ “ያስተማርኩት፣ የጻፍኩ ትና የተናገርኩት ሁሉ ስሕተት መሆ ኑን ስላመንኩ ይህን ሁሉ ስሕተቴን ቅዱስ ሲኖዶስ ተረድቶልኝ ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ትምህርቱን እንድ ማር ይፈቀድልኝ ዘንድ በታላቅ ትሕ ትና አመለክታለሁ የሚል የይቅርታ [አሳብ] እንደሌለኝ በድጋሚ አረጋግጣለሁ” የሚል የትዕቢት ደብዳቤ ነው፡፡ ተሐድሶ መናፍቃን በተለያዩ ዘዴ ዎች ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያስተላልፋቸ ውን ውሳኔዎች ሲቃወሙና በቻሉት መጠን ለተቃውሟቸው ድጋፍ የሚሰጡ አካላትን በቤተ ክስቲያን መዋቅር ውስጥ አሥርገው ለማስገባት ሲሠሩ ቆይተዋል፡፡ ይኸው ዓላማቸው ተሳክቶ ላቸው በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ የቤተ ክርስቲያንን እንጀራ እየበሉ የቅ ዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ በፊርማ ለማስ ቆም የሚሠሩ ጥቂት አካላትን ማግ ኘት ችለዋል፡፡ ለዚህም ነው ተሐድሶ መናፍቃን በተለያዩ ድረ ገጾቻቸው የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ አንቀበልም በማለት ከመጻፍ እና ከመሳደብ አል ፈው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር አሥርገው ባስገቧቸው አንዳ ንድ ግለሰቦች በኩል የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔዎች ለማስቀልበስ እየ ሠሩ ያሉት፡፡
ይህን ዓላማቸውን ዕውን ለማድ ረግ በተለይም በመንፈሳዊ ኮሌጆች ውስጥ አሥርገው ባስገቧቸው አንዳንድ ተልእኮ አስፈጻሚ ግለሰቦች በኩል እነ ርሱ የማይፈልጉትን የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ለመቃወም መምህራንን፣ ተመር ቀው የወጡና በመማር ላይ ያሉ የነ ገረ መለኮት ደቀ መዛሙርትን እና ጉዳዩ የማይመለከታቸው የዋሀን ምእመናንን ፊርማ እንዲያሰባስቡላቸው እየተጠቀሙባቸው ይገኛሉ፡፡ ይህም ድር ጊት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጣቸው መመ ሪያዎችና የሚወስናቸው ውሳኔዎች ተግባራዊ ቢደረጉ ለእንቅስቃሴያቸው እንቅፋት እንደሚሆንባቸው በማመን አቅጣጫ ለማስቀየርና ለማደናገር የሚ ጠቀሙበት ስውር ስልት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን፣ ቅዱስ ሲኖዶስን፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳ ሳትን እንደፈለጋቸው ሲሳደቡ የሚጠ ይቃቸው አካል ባለመኖሩ ምክንያት የልብ ልብ ተሰምቷቸው የሚፈጽሙት የዕብሪት ተግባር ነው፡፡ ተሐድሶ መና ፍቃን መናፍቅነታቸውን በራሳቸው ጽሑ ፎች አውጀው፣ የራሳቸውን የእምነት ድርጅት አቋቁመውና የራሳቸውን የእምነት መግለጫ አውጥተው ቤተ ክር ስቲያንን የማፍረስ ተልእኳቸውን ዕውን ለማድረግ እየሠሩ መሆናቸው እየታ ወቀ “ዐይናቸውን በጨው አጥበው” አሁንም ኦርቶዶክሳውያን ነን በማለት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሠርገው በመግ ባት ሁከት እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያንን ሰላም የማይወዱት እነዚህ አካላት በአንጻራዊ መረጋጋት ላይ ይገኙ የነበሩትን መንፈሳዊ ኮሌጆችን አሥር ገው ባስገቧቸው ጥቂት ተላላኪዎች አማካኝነት በተለያዩ የስድብ አፎቻቸው ሲያጮኹት የኖሩትን ዓላማ ለማሳካት ሊጠቀሙባቸው በስውር በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጠቃ ላይ በቤተ ክርስቲያን ላይ በተለይ በመ ንፈሳዊ ኮሌጆች ላይ የተነጣጠረው የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ አሳሳ ቢና አስጊ መሆኑን ተረድቶ ኮሚቴ አቋ ቁሞ ሥራዎችን መሥራት በጀመረበት በዚህ ወቅት፣ መንፈሳዊ ኮሌጆችም ስንዴ ውን ከገለባው የማጥራት ሥራ ለመሥ ራት በጀመሩበት ጊዜ፣ ሰንበት ትምህ ርት ቤቶችና ወጣቶችም ተሐድሶ መና ፍቃንን በማጋለጥ መረጃዎችን በማሰባ ሰብ ለሚመለከተው አካል እያቀረቡ ባሉበት በዚህ ሰዓት “መናፍቅ የሚባል ነገር የለም” በማለት የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔ ለማኮላሸት ፊርማ የሚያ ሰባስቡ አካላት መነሣታቸው እየተሰማ ነው፡፡ ይህ ድፍረት ከቤተ ክርስቲያን ዓላማ መውጣትና ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳ ኔም አለመታዘዝ ነው፡፡
ተሐድሶ መናፍቃን ቤተ ክርስቲ ያን ውስጥ አንድ ችግር ፈጥረው መዋ ቅሩ ችግሩን ለመፍታት ደፋ ቀና በሚል በት ሰዓት እነርሱ የራሳቸውን ዓላማ ለማሳካት መሯሯጥን ልምድ አድርገው ሲሠሩበት የቆዩት ጉዳይ ነው፡፡ ቅድ ስት ቤተ ክርስቲያን የመልካም አስተዳ ደር እጦት መኖሩን አምና የመልካም አስተዳዳር ችግሮችን ለመቅረፍ መሥ ራት አለብን በሚል በሁሉም አህጉረ ስብከት በሚባል ደረጃ ውይይቶች እየተደረጉና ሥልጠናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም በጥቅምት ፳፻ወ፰ ዓ.ም መደበኛ ጉባኤ ባወጣው መግለጫ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና መስፋፋት ለቤተ ክርስቲያን ፈተና መሆ ኑን እና የችግሩ መነሻና ምንጭ ይታ ወቅ ዘንድ አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያ ኗን ሁለንተናዊ ችግር የሚያጠና ብፁ ዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ዐቢይ ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የመልካም አስተዳደር ችግር የአ ንድ ተቋም ችግር ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ መዋቅሮች ላይ የሚታይ አጠቃላይ ችግር መሆኑን ወስኖ እያለ ተሐድሶ መናፍቃን የአስተ ዳደር ችግር አለ ሲባል ለራሳቸው ዓላማ በሚጠቅማቸው መልኩ ሌላ ቅርጽ ሰጥተውና ስድብ አስመስለው ጉዳዩን ያስተጋቡልናል ብለው ለሚያስ ቧቸው አካላት ያቀርቡላቸዋል፡፡ ይህን የመናፍቃን ተንኮል ያልተረዱ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሓላፊነት ያላቸው አንዳንድ ግለሰቦችም የመልካም አስተዳዳር ችግር አለ መባሉን መናፍቅ ናችሁ የመባል ያህል ይፈሩታል፡፡ ይህ ግን በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ ታምኖበት ለውጥ ለማምጣት እየተሠራበት ያለ መሆኑን ማንም የማይስተው ሐቅ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መልካም ነገር መስማት የማይፈልጉት ተሐድሶ መናፍቃን ግን በቤተ ክርስቲያን ደረጃ የታመነውን እውነት የተለያዩ የቤተ ክርስቲያን ተቋማትን በመምራት ላይ ለሚገኙ አካላት “እንዲህ ተብላችሁ ተሰ ደባችሁ” በማለት የሐሰት ክስ በማቅረብ የቤተ ክርስቲያን ችግሮች ተፈተው ለውጥ እንዳይመጣ ይሠራሉ፡፡
በአጠቃላይ ተሐድሶ መናፍቃን በተለ ያዩ የስድብ አፎቻቸው የሚጮኹትን ጩኸት የሚሰማቸው አካል ባለማግኘታ ቸው ምክንያት ወደ ቤተ ክርስቲያን አሥርገው ባስገቧቸው አንዳንድ አካ ላት በኩል የራሳቸው ድብቅ ዓላማ ያላቸው ጥቂት ግለሰቦችን በማባበል ከውጪ ሆነው ሲጮኹለት የነበረውን ዓላማቸውን ለማስፈጸም ይጠቅመናል ብለው ያሰቡትን ማደናገሪያ ሁሉ ለመጠ ቀም እየሞከሩ ነው፡፡ ይህም ለቤተ ክርስቲያን ተቆርቋሪ በመምሰል በየጊ ዜው የሚፈጠሩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ተጠ ቅመው አቅጣጫ በማስቀየር ለዓላማ ቸው ማስፈጸሚያነት የሚጠቀሙበት የተለመደ ስልት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የራሷ ሥርዓትና መዋቅር ያላት፣ ውሳኔ ዎችን የምትወስነው ከሐዋርያት ጀምሮ በተሠራ ሕግና ሥርዓት በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥንቃቄ እና በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ሆኖ ሳለ ተሐድሶ መናፍቃን የቅዱስ ሲኖዶ ስን ውሳኔ በግለሰ ባዊ ዓላማ ለማስቀ ልበስ እየተሯሯጡ መሆናቸው ጥፋታ ቸውን አምነው ከመመለስ ይልቅ ኑፋ ቄያቸው በቤተ ክርስቲያን ዕውቅና እን ዲሰጠው ለማድረግ መሞከር ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን የመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካል በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አለመታዘዝ ትዕቢትም ኑፋቄም ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ተሐድሶ መናፍቃን ብዙ የዋሀንን ለማደናገርና ተባባሪ ለማ ብዛት የሚጠቀሙበት ስልት እውነቱ ተደብቆ ሐሰቱ እውነት መስሎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሠርጎ እንዲገባ ማድረግ በመሆኑ ይህን የጥፋት ተልእኮ ለመግ ታት ሁሉም አካላት ሊተባበሩበት ይገ ባል፡፡ 

 

Read more http://www.eotcmk.org/site/-mainmenu-24/--mainmenu-26/2060-2016-01-06-deferet-esek-sinode