በዚህ በምንኖርበት በውጪው ዓለም በወርኃ ኅዳር «የምስጋና ቀን» በሚል ስያሜ ቤተሰብ ተሰባስቦ እየተበላና እየተጠጣ በዓሉ ይከበራል። ዓመቱን በሙሉ በቀን ሃያ አራት ሰዓት ክፍት ሆነው አገልግሎት የሚሰጡ የንግድ ቦታዎች ሳይቀሩ በዚህ ቀን ይዘጋሉ። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመቱን በሙሉ በምስጋና አጥሮት በእያንዳንዱ ቀን ዓለማትን ለፈጠረ ለእግዚአብሔር ምስጋና እንዲገባ ለዕለቱ ተስማሚ የሆነውን ቃለ እግዚአብሔር በመምረጥ ከሌላው የዓለም ሕዝብ በተለየ ኢትዮጵያውያን በምስጋና እንዲኖሩ የሚችሉበትን ሁኔታ አመቻችቷል።