Print

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የርእሰ አድባራት ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤዛ-ኵሉ ሰንበት ት/ቤት የተመሠረተበትን ታሪካዊ ፳ኛ ዓመታዊ በዓሉን በተለያዩ መንፈሳዊ ዝግጅቶች ከቤተ ክርስቲያናችን እና ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ተጋብዘው ከሚመጡ ካህናት ጋር በመሆን ለማክበር ተዘጋጅቷል።

 

ቦታ፡ ርእሰ አድባራት ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል (2601 Minnehaha Ave. Minneapolis, MN 55406)

 

መቼ፡ ከአርብ ሐምሌ ፲፭ እስከ እሑድ ሐምሌ ፲፯/፳፻፰ ዓ.ም. (July 22-24, 2016)

 

በመርሐ ግብሩ ከሚካተቱት የትምህርት፣ የመዝሙር፣ የሥነ-ጽሑፍ፣ የዐውደ ርእይ እና የመሳሰሉት በርካታ ዝግጅቶች መካከል እሑድ ሐምሌ ፲፯/፳፻፰ ዓ.ም. (July 24, 2016) "የኢዮብ መከራ እና የእግዚአብሔር ቸርነት" በሚል ርእስ የተዘጋጀ ተውኔት ይቀርባል።