በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የርእሰ አድባራት ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤዛ-ኩሉ ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ የስድስት ወራት የሃይማኖት ትምህርት  ዘወትር ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ከ 4:00 P.M. – 6:00 P.M. ከጥር ፳፻፱ ዓ/ም (January 2017) ጀምሮ ለመስጠት ተዘጋጅቷል። ይኽ ኮርስ በርእሰ አድባራት ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የስብከተ ወንጌል ክፍል እና ቤዛ-ኩሉ ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ በዓይነቱ የመጀመርያ ሲሆን ኮርሱም በደብሩ ካህናት እና በሰ/ ት/ቤት አገልጋዮች ይቀርባል፤ በኮርሱ ፍጻሜም የመመረቂያ ምስክር ወረቀት ይሰጣል። የትምህርቱ ርእሶች፦

የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በታላቅ ፍሥሐ እና ይባቤ ለማክበር የፈቀደልን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። ከሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በረከት ረድኤት ይክፈለን። እስራኤልን በመንገዳቸው የረዳቸው እኛንም ከክፉ ነገር ሁሉ በክንፎቹ ጋርዶን ይጠብቀን። ይኽንን ታላቅ በዓል ለማክበር ሁላችን ከዋዜማው ጀምረን እንድንገናኝ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።