ትንሣኤ ማለት ምን ማለት ነው? ትንሣኤ ማለት ነፍስና ሥጋ ተለያይተው ከኖሩ በኋላ ሁለተኛ ተዋሕደው መነሣት ማለት ነው። ትንሣኤ ለምን ሆነ? ሰው የተፈጠረው ነፍስና ሥጋው  ሳይለያዩ  በሕይወት ለመኖር እንጂ ለሞት አልነበረም፤ እግዚአብሔር ሞትን አልፈጠረምና። ኗሪ ይሆን ዘንድ ፍጥረትን ፈጥሮአልና የሰዎች ጥፋት ደስ አያሰኘውም። መፈጠራችን ለድኅነት ነውና ሕይወት የማታልፍ ስለሆነች ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እግዚአብሔር ለሞት አላደረገነምና ለሕይወት እንጂ ፩ተሰ ፭፥፱ ይለናል።