የንባብ ምልክቶች

ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም.

መ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር

  • የማንሳት ምልክት

  • የመጣል ምልክት

  • የማጥበቅ ምልክት

አንዳንድ የግእዝ ግሶች የሚጠብቅ ድምፅ ሲኖራቸው ግማሾቹ የላቸውም፡፡


ምሳሌ፣ ቀተለ -- ገደለ፣ ቀደሰ -- አመሰገነ


ትውውቅ


ሰላም ለከ አኁየ                     ወ ሰላም ለከ


(ሰላም ላንተ ይሁን ወንድሜ)       (ሰላም ላንተም ወንድሜ)


መኑ ስምከ እኁየ                    ወልደ ገብርኤል ውእቱ ስምየ


(ስምህ ማን ነው ወንድሜ)         (ስሜ ወልደ ገብርኤል ነው)


ወመኑ ስመ አቡከ                  ገ/ ማርያም ውእቱ ስመ አቡየ


(ያባትህ ስም ማን ነው)            (ያባቴ ስም ገ/ማርያም ነው)


እስፍንቱ አዝማኒከ                  እሥራ ወአሐዱ


(ዕድሜህ ስንት ነው)               (ሀያ አንድ)


እም አይቴ መጻእከ                      እም ጎጃም


(ከየት መጣህ)                        (ከጎጃም)


ግብር እፎ ውእቱ                      ሚመ ኢይብል


(ሥራ እንዴት ነው)                  (ምንም አይል)


እስኩ ነዓ ነሑር ኀበ ቤተ እግዚአብሔር    ትፍስሕትየ ውእቱ


እስኪ ና ወደ ቤተክርስቲያን እንሂድ       (ደስታዬ ነው)


ሕይወት እፎ ውእቱ                      ሠናይ ውእቱ


(ሕይወት እንዴት ነው)                  (ጥሩ ነው)


እሉ አብያፂከ ውእቶሙ                    እወ


(እነዚህ ጓደኞችህ ናቸው)                (አዎ)


አይቲ ብሔሮሙ                          (ዝ እም ሲዳሞ ወዝኩሰ እም ወሎ)


(የት ነው ሀገራቸው)                     (ይህ ከሲዳሞ ነው ያ ደግሞ ከወሎ)


ትትሜህርኑ ትምህርተ ዘመነዌ              እወ እትሜሀር አነ ትምህርተ ዘመነዌ


(የዘመናዊ ትምህርት ትማራለህ)            (አዎ የዘመናዊ ትምህርት እማራለሁ)


አይቴ ውእቱ ቤተ ትምህርትከ               6 ኪሎ ውእቱ ቤተ ትምህርትየ


(ትምህርት ቤትህ የት ነው)                (6 ኪሎ ነው ትምህርት ቤቴ)


ስፍነ አመተ በጻሕከ                        ሣልሳ ዓመተ በጻሕኩ


(ስንተኛ ዓመት ደረስክ)                    (3 ዓመት ሆኖኛል)


ተአምርኑ ትምህርተ ሃይማኖትከ ወ ሀገርከ      ምንት ውእቱ ትምህርተ ሀገርየ


(የሀይማኖትህ እና የሀገርህን ትምህርት ታውቃለህ)     (የሀገሬ ትምህርት ምንድን ነው)


ንባብ፣ ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ግእዝ፣ ቅኔ ይትበሀሉ       ለእሉሰ አኣምሮሙ ቀዲሙ


(ንባብ፣ ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ይባላሉ)                 እነሱን ቀድሞ አውቃቸዋለሁ


በል እግዚእ የሀብከ ጽንአቶ ወይክስት ለከ           አሜን


(በል ጌታ ፅናትን ይስጥህ ይግለፅልህም)           (ይሁን ይደረግልኝ)

 

ግሥ አርዕስት (Root Verbs)

 

የግሥ አርዕስት ማለት ለሌሎች ግሶች መሠረት በመሆን የሚከተሏቸው ግሶች የእነርሱን የአወራረድ ባህሪ የሚከተሉ እና በአቀማመጣቸው የሚመስሏቸው ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሁሉ ግልፅ የሚሆኑት በዝርዝር ሥንመለከታቸው በመሆኑ በመጀመሪያ ግር ሊለን አይገባም፡፡ የሆነው ሆኖ ለግስ ርባታ መሠረት መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ የታወቁት የግስ አርዕስታት ስምንት ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸውም የየራሳቸው ሠራዊት አላቸው፡፡


1. ቀተለ    2. ቀደሰ    3. ገብረ    4. አእመረ   5. ባረከ   6. ሤመ    7. ብህለ         8. ቆመ
6.1 እርባ ግስ (Tense and Nouns formation, including Adjectives)


በመጀመሪያ ግን አንድ በአንድ የስምንቱን ግሶች ቀለማት ብዛትና ዓይነት አንባቢው ማስተዋል ይገባዋል፡፡

  1. ቀተለ ፍፁም ሁሉም ግእዝ ሆኖ የላላ

  2. ቀደሰ ፍፁም ግእዝ ሆኖ የጠበቀ

  3. ገብረ ግእዝ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  4. አእመረ ግእዝ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  5. ባረከ ራብዕ ግዕዝ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  6. ሤመ ኀምስ ግእዝ ሆኖ የላላ

  7. ብህለ ሳድስ ሳድስ ግዕዝ ሆኖ የላላ

  8. ቆመ ሳብዕ ግእዝ ሆኖ የላላ

ማንኛውም የቀዳማይ አንቀፅ ግስ ሁሉ ተነሽ መሆኑን በሥርዓተ ንባብ ላይ አይተናል፡፡

1. ቀተለ ---- ገደለ ( past tense - ሐላፊ) / ቀዳማይ አንቀፅ/

ይቀትል --- ይገድላል (future- ካልአይ--- ትንቢት ወይም Present Tense - ያሁን ጊዜ)

ይቅትል ---- ይገድል ዘንድ / ዘንድ አንቀፅ/

  • ቀቲል / ቀቲሎት/ -- መግደል/ to kill ( infinitive) ንዑስ አንቀፅ/

ቀታሊ -- የገደለ / ቅጽል --Adjective


ቀታልያን--- የገደሉ /ወንዶች/ / ቅጽል ሲበዛ/


ቀታሊተ --- የገደለች / ለሴት ቅጽል ሲሆን


ቀታልያት --- የገደሉ / ለብዙ ሴቶች ቅጽል ሲሆን/


ቅቱል ---- የተገደለ / ቅጽል -- Adjective/


ቀታሊ ----ገዳይ / ስም ሲሆን/


ቀትል --- ውጊያ / ጥሬ ዘር/


ቅትለት --- አገዳደል / ሳቢዘር/


በ ቀተለ ምሳሌ እንሰራና ሌሎችን እንዴት እንዳሚወርዱ ካየን በኋላ ሌሎችን በራሳችን መሥራት እንችላለን፡፡


ምሳሌ፡-

አነ ቀተልኩ -- እኔ ገደልኩ


አነ እቀትል --- እኔ እገድላለሁ


አነ እቅትል--- እገድል ዘንድ/ ዘንድ አንቀፅ/


አነ እቅትል --- ልግደል / ትዕዛዝ/


አንተ ቀተልከ --- አንተ ገደልክ አንቲ ቀተልኪ---- ገደልሽ


አንተ ትቀትል --- አንተ ትገድላለህ አንቲ ትቀትሊ--- ትገድያለሽ


አንተ ቅትል----- አንተ ግደል አንቲ ትቅትሊ ---- ትገድይ ዘንድ


ንህነ ቀተልነ --- ገደልን አንቲ ቅትሊ --- ግደዬ


ንህነ ንቀትል --- እንገድላለን አንትን ቀተልክን --- ገደላችሁ /ሴ/


ንህነ ንቅትል --- እንገድል ዘንድ አንትን ትቀትል ---- ትገድላላችሁ / ሴ/


ንህነ ንቅትል --- እንግደል አንትን ትቅትል---- ትገድሉ ዘንድ /ሴ/


አንትሙ ቀተልክሙ ---ገደላችሁ /ወ/ አንትን ቅትል ---- ግደሉ /ሴ/


አንትሙ ትቀትሉ ----ትገድላላችሁ/ወ/ ውእቶሙ ቀተሉ --- ገደሉ /ወ/


አንትሙ ትቅትሉ ---ትገድሉ ዘንድ/ወ/ ውእቶሙ ይቀትሉ ----ይገድላሉ/ወ/


አንትሙ ቅትሉ ---- ግደሉ/ወ/ ውእቶሙ ይቅትሉ --- ይገዳሉ ዘንድ/ወ/


ውእቱ ቀተለ --- ገደለ ውእቶሙ ይቅትሉ ---- ይግደሉ/ወ/


ውእቱ ይቀትል ----- ይገድላል ይእቲ ቀተለት ---- ገደለች


ውእቱ ይቀትል ---- ይገድል ዘንድ ይእቲ ትቀትል --- ትገድላለች


ውእቱ ይቅትል ---- ይግደል ይእቲ ትቅትል --- ትግድል ዘንድ /ሴ/


ውእቶን ቀተላ --- ገደሉ /ሴ/ ይእቲ ትቅትል--- ትግደል


ውእቶን ይቅትላ ---- ይገድላሉ /ሴ/


ውእቶን ይቅትላ --- ይገድሉ ዘንድ /ሴ/


ውእቶን ይቅትላ --- ይግደሉ /ሴ/


ማስታወሻ፣ ሀ. የትንቢት( future) እና የአሁን ጊዜ( Present) በግእዝ


አንድ ዓይነት የግሥ አወራረድ / አገባብ/ አላቸው፡፡

ለ. ዘንድ አንቀጽና ትዕዛዝ አንቀጽም እንዲሁ አንድ ዓይነት ናቸው፡፡


ሐ. የእግዝ ግሶች ርባታቸውን የሚጀምሩት በቀዳማይ አንቀጽ (past) ነው፡፡


ቀተለን የሚመስሉ ግሶች ነበረ፣ ወረደ፣ ወዘተ ናቸው፡፡ ነገር ግን አወራረዳቸው ከቀተለ ሊለዩ ስለሚችሉ ማስተዋል ያስፈልጋል ፡፡


ምሳሌ ወረደ፣ ይወርድ፣ ይረድ

 

Read more http://www.eotcmk.org/site/--mainmenu-56/1552-2014-09-05-09-22-24