ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ። (፩ጴጥ. ፪፡፳፬)

 

የበዓላት አከባበር ፍጹም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው። በዓላት የሰው ልጆች እግዚአብሔርን የሚያከብሩበት አንደኛው መገለጫቸው ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን ከማመስገን የተቆጠበችበት ጊዜ ባይኖርም በበዓላት ግን በበለጠው ስያሜው በተሰየመላቸው ቅዱሳን አማካኝነት የእግዚአብሔር ሥራው ይነገርበታል። በርካታ በዓላት በቅድስት አገር ኢትዮጵያ እንደሚከበረው እኛም በደብራችን ቅድስት ሥላሴን መድኃኔዓለምን፣ ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ዮሐንስን እናከብራለን።

 

 

በመሆኑም የዛሬ ወር በደብራችን የጥቅምት መድኃኔዓለም ንግሥ ስለሚኖር ምእመናን ከወዲሁ ጊዜያችሁን አመቻችታችሁ የበዓሉ ተሳታፊ እንድትሆኑ ከወዲሁ እናስታውቃችኋለን።

 

ቅዳሜ በዋዜማው ሰዓት እና እሑድ በንግሡ ሰዓት ተገኝተን ዓለምን በክቡር ደሙ ያዳነውን ኢየሱስ ክርስቶስን በማሕሌት፣ በቅዳሴና በዝማሬ እናመስግነው። የጊዜ ባለቤት ሁላችንንም በሰላም በጤና ጠብቆ የቀጠሮ ሰው ይለን ዘንድ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን።

 

 

 

 ከበዓሉ በረከት ተሳታፊ ያደርገን ዘንድ ልዑል እግዚአብሔር በጤና ይጠብቀን፤

 

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ጸሎት አይለየን።

 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ወለመስቀሉ ክብር ወለወላዲቱ ድንግል

 

ወ/ት ዘመናይ ዘሪሁን