መዝሙር (አቤት የዚያን ጊዜ) March 31, 2019
አቤት የዚያን ጊዜ ክርስቶስ ሲመጣ /፪/
ትንሹም ትልቁም /፫/ መድረሻውን ሲያጣ
ከምሥራቅ ከምዕራብ ከሰሜን ከደቡብ /፪/
ነፋሳት ሲላኩ /3/ መዓትን ለማዝነብ
ሰማይና ምድር በአንድ ሲዋሐዱ /፪/
የት ይሆን መድረሻው /፫/ የት ይሆን መንገዱ
አቤት የዚያን ጊዜ ክርስቶስ ሲመጣ /፪/
ትንሹም ትልቁም /፫/ መድረሻውን ሲያጣ
ከምሥራቅ ከምዕራብ ከሰሜን ከደቡብ /፪/
ነፋሳት ሲላኩ /3/ መዓትን ለማዝነብ
ሰማይና ምድር በአንድ ሲዋሐዱ /፪/
የት ይሆን መድረሻው /፫/ የት ይሆን መንገዱ
አድኚኝ እናቴ ከሥጋ ፈተና
ሥጋዬ ከኃጢአት ከቶ አልራቀምና
ሸክሜ የከበደኝ ብቸኛ ሆኛለሁ
አትለይኝ ድንግል አደራ እልሻለሁ /፪/
የአማኑኤል እናት የተዋሕዶ አክሊል
አትጥፊ ከመሃል እንድትሆኚን ኃይል
ምንም ቢበዛብሽ የእኛ ጉስቊልና
ከእኛ ጋራ ከሆንሽ አለን ቅድስና /፪/
እንደ በደሌማ ከሆነ ቅጣቴ
አያልቅም ተነግሮ ብዙ ነው ጥፋቴ
እንጃልኝ ፈራሁኝ አዬ ሰውነቴ(፪)
እመ አምላክ /፪/ አስቢኝ በሠርክ
ኀዘኔ ጭንቀቴ በጣም በዛብኝ
ከልጅሽ አስታርቂኝ አንቺው አማልጂኝ
ከመንበሩ ቆመሽ ንገሪው ለልጅሽ
እናቱ ነሽና እርሱ አያሳፍርሽ
እመ አምላክ /፪/ አስቢኝ በሠርክ
ሞተሃልና ስለእኔ ምንም ሳይኖርብህ ጥፋት
ተከሰህ ተወቅሰህ በጲላጦስ ፊት
ኢየሱስ አምላከ ምሕረት ስብሐት ለከ
ስላላወቁህ አንተን የዓለም መድኃኒት መሆንህን
መቱህ በጭካኔ ብርሃን ፊትህን
ኢየሱስ መድኃኒታችን ስብሐት ለከ