መዝሙር (የጠሩሽ) December 30, 2018
የጠሩሽ አንቺን ተማፅነው የዳኑብሽ
የበላዔ ሰብ እመቤት የአምላክ እናት
ድንግል አዛኝቱ ማርያም ቅድስት(፪)
በቃል ኪዳንሽ ብዙዎች ድነዋል
በምልጃሽም ፅድቅን አግኝተዋል
የአምላክ ቸርነቱን አይተዋል(፪)
የጠሩሽ አንቺን ተማፅነው የዳኑብሽ
የበላዔ ሰብ እመቤት የአምላክ እናት
ድንግል አዛኝቱ ማርያም ቅድስት(፪)
በቃል ኪዳንሽ ብዙዎች ድነዋል
በምልጃሽም ፅድቅን አግኝተዋል
የአምላክ ቸርነቱን አይተዋል(፪)
ትምክሕተ ዘመድነ /፪/ ማርያም እምነ
ማርያም ትምክሕተ ዘመድነ
የድኅነታችን ዓርማ የነፃነታችን
የሕይወት መሠረት ነሽ ድንግል እናታችን
አንቺን ለእኛ ዘርን ባያስቀር
እንደ ጥንቱ እንደ ሰዶም ምድር
ሁላችን በጠፋን ነበር
ሠርዓ ለነ ሰንበተ ለእረፍተዚአ (፪)
ሠርዓለነ ሰንበተ ለእረፍተዚአ ኧኸ ሠርዓለነ ሰንበተ ለእረፍተዚአ
ሠራልን ሰንበትን ለእረፍታችን (፪)
ሠራልን ሰንበትን ለእረፍታችን ኧኸ ሠራልን ሰነበትን ለእረፍታችን
በስድስቱ ቀናት ሁሉን ነገር ሰርቶ
ሰባተኛው ቀን ለእረፍት አዘጋጅቶ
ለሁላችን ሰጠን ከቀናት ለይቶ
ሠርዓ ለነ ሰንበተ ለእረፍተዚአ ኧኸ ሠርዓለነ ሰንበተ ለእረፍተዚአ
ዘየአምር እምቅድመ ኅሊና ዘይሄሊ ልበ የአምር (፪)
አርዓየ ኃይሎ በላእሌነ ወጸገወነ ኧኸ ሰናይቶ እግዚአብሔር (፪)
ትርጉም ፦ልብ ያሰበውን ከህሊና አስቀድሞ ያውቃል
እግዚአብሔር ኃይሉን በላያችን አሳይቶ መልካሙን ሰጠን
ምን ሰማህ ዮሐንስ በማህጸን ሳለህ (፪)
ህፃን ሆነህ ነቢይ ለክብር የተጠራህ (፪)
እንደ እንቦሳ ጥጃ ያዘለለህ ደስታ (፪)
ምን አይነት ድምፅ ነው ምን አይነት ሰላምታ (፪)
ከተፈጥሮ በላይ ያሰገደህ ክብር
እንዴት ቢገባህ ነው የእናታችን ፍቅር (፪)
ሌላ ድምፅ አልሰማም ከእንግዲህ በኋላ
ለውጦኛልና የሰላምታ ቃሏ (፪)