መዝሙር (ድንግል መከራሽን) October 14, 2018


 ድንግል መከራሽን
 ድንግል መከራሽን ጥቂት ባስታውሰው
 በሄሮድስ ዘመን ፍጥረት ያለቀሰው
 አንቺ የአምላክ እናት ደግሞም እመቤት
 እንደ ችግረኛ ተነሳሽ ስደት(፪)

ኧረ ለመሆኑ እንዴት አለቀልሽ
ስትከራተቺ በረሃውን ቆርጠሽ
ይገሉታል ብለሽ ለልጅሽ አስበሽ
በሄሮድስ ዘመን መከራሽን አየሽ (፪)

መዝሙር (ጻድቃን ሰማእታት) September 30, 2018


 ጻድቃን ሰማእታት በሙሉ በአካለ ሥጋና በአካለ ነፍስ /፪/ ያሉ
 ከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉ

የእግዚአብሔር ዐይኖቹ ጻድቃንን ከማየት
ጆሮዎቹም አይርቁም እነርሱን ከመስማት
የጻድቅ ሰው ጸሎት ኃይልን ታደርጋለች
በምልጃቸው እንመን አናመንታ በአንዳች

 ጻድቃን ሰማእታት በሙሉ በአካለ ሥጋና በአካለ ነፍስ /፪/ ያሉ
 ከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉ

ጊዜያዊው ፈተና ሳያሳቅቃቸው
እሳትና ስለት ሳያስፈራራቸው
ሰማያዊው ተስፋ ስለሚታያቸው
በፈተና ሁሉ ጸኑ በእምነታቸው

 ጻድቃን ሰማእታት በሙሉ በአካለ ሥጋና በአካለ ነፍስ /፪/ ያሉ
 ከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉ

ኃጥኡ ነዌ እንኳን በሲዖል እያለ
ስለወንድሞቹ ምህረት ከለመነ
እናንተማ ጻድቃን በገነት ያላችሁ
ምንኛ ትረዱን አምነን ስንጠራሁ

 ጻድቃን ሰማእታት በሙሉ በአካለ ሥጋና በአካለ ነፍስ /፪/ ያሉ
 ከፈጣሪ አማልደው እኛን ያስምራሉ

ቀዝቃዛ ውኃ እንኳን በጻድቅ ሰው ስም
የሚያጠጣ ቢኖር ዋጋው አይጠፋም
ብሎ እንዳስተማረን ጌታ በወንጌል
አምነን እንፈጽመው ዋጋ ያሰጣል

መዝሙር 3 (ዝም አትበሉ) September 22, 2018


 ዝም አትበሉ እግዚአብሔርንአመስግኑ/፪/
 ቅዱስ/፭/ በሉ መላእክትን ሁኑ ምስጋናን ጨምሩ ቅዱስ/፪/ በሉ

የሙሴ እህት ማርያም ከበሮውን አንሽው
በምስጋና መዝሙር እስራኤልን ጥሪው
አምላክን እናክብር እንዘምር በእልልታ
ከእኛ ጋር ይሆናል የሰራዊት ጌታ ፪

 ዝም አትበሉ እግዚአብሔርንአመስግኑ/፪/
 ቅዱስ/፭/ በሉ መላእክትን ሁኑ ምስጋናን ጨምሩ ቅዱስ/፪/ በሉ

ፍጥረታትም ጩሁ ሰማያት ዘምሩ
ስለቅድስናው ውዳሴን ጨምሩ
ዳዊት ሆይ ተነሳ ስለፅዮን ዘምር
ከበሮው ይመታ በገናው ይደርደር ፪

 ዝም አትበሉ እግዚአብሔርንአመስግኑ/፪/
 ቅዱስ/፭/ በሉ መላእክትን ሁኑ ምስጋናን ጨምሩ ቅዱስ/፪/ በሉ

ወገኖች እንዘምር ለእግዚአብሔር ክብር
ውለታው ብዙ ነው ለእኛ ያለው ፍቅር
ማዳኑን ያያችሁ ዘምሩ በእልልታ
ለጌታ ለእግዚአብሔር ለሰራዊት ጌታ ፪

 ዝም አትበሉ እግዚአብሔርንአመስግኑ/፪/
 ቅዱስ/፭/ በሉ መላእክትን ሁኑ ምስጋናን ጨምሩ ቅዱስ/፪/ በሉ

ባህሩን አቋርጦ ወንዝ ያሻገራችሁ
ተራራውን ንዶ ያቀለለላችሁ
በአውሎ ነፋስ መሀል መንገድ አለው ጌታ
ለንጉስ ክርስቶስ እንዘምር በእልልታ ፪

 ዝም አትበሉ እግዚአብሔርንአመስግኑ/፪/
 ቅዱስ/፭/ በሉ መላእክትን ሁኑ ምስጋናን ጨምሩ ቅዱስ/፪/ በሉ

መዝሙር 2 (ደስ ይበለን) September 22, 2018


 ደስ ይበለን ደስ ይበለን
 አምላክ አለ መሃላችን
 ምን ይከፈል ለዚህ ሥራህ
 ገናና ነው አምላክ ክብርህ፤

ምሕረቱ አይተናልና
አድርሶናል አምላክ በጤና
ይችን እድሜ የጨመረልን
ለንስሐ ጊዜ የሰጠን

 ደስ ይበለን ደስ ይበለን
 አምላክ አለ መሃላችን
 ምን ይከፈል ለዚህ ሥራህ
 ገናና ነው አምላክ ክብርህ፤

ኃጢአትህ ይታገሰሃል
በቸርነት አምላክ ያይሃል
ደስታ ነው በሰማያት
በአንድ ኃጥእ የጽድቅ ሕይወት

 ደስ ይበለን ደስ ይበለን
 አምላክ አለ መሃላችን
 ምን ይከፈል ለዚህ ሥራህ
 ገናና ነው አምላክ ክብርህ፤

እልል በሉ የጐበኛችሁ
በምሕረቱ አምላክ ያያችሁ
በችግር ቀን ያሰበን ሁሉ
አመስግኑ ዝምም አትበሉ

 ደስ ይበለን ደስ ይበለን
 አምላክ አለ መሃላችን
 ምን ይከፈል ለዚህ ሥራህ
 ገናና ነው አምላክ ክብርህ፤

ድንግል ማርያም ትጸልያለች
ኃጥኡን ሰው ማረው እያለች
በድንግል ክብር እንኖራለን
በጽኑ ፍቅር አንድ እንዲያደርገን

 ደስ ይበለን ደስ ይበለን
 አምላክ አለ መሃላችን
 ምን ይከፈል ለዚህ ሥራህ
 ገናና ነው አምላክ ክብርህ፤

መዝሙር (ንሴብሖ) September 22, 2018


 ንሴብሖ/፪/ ለእግዚአብሔር/፪/
 ስቡሐ ዘተሰብሐ/፪/
 እናመስግነው/፪/ እግዚአብሔርን
 ምስጉን ነው የተመሰገነ/፪/

ባሕሩን ተሻግረን ወንዙ ደረቅ ሆነ
በጠላታችን ላይ ድሉ የኛ ሆነ
ከባርነት ቀንበር ፍጹም ነጻ ወጣን
ሕይወት የሚሰጠን መና ነው ምግባችን

 ንሴብሖ/፪/ ለእግዚአብሔር/፪/
 ስቡሐ ዘተሰብሐ/፪/
 እናመስግነው/፪/ እግዚአብሔርን
 ምስጉን ነው የተመሰገነ/፪/

አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር
ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር
ጉልበታችን ቢዝል ፈተናው ቢበዛ
ኃይላችን ጌታ ነው የዓለሙ ቤዛ

 ንሴብሖ/፪/ ለእግዚአብሔር/፪/
 ስቡሐ ዘተሰብሐ/፪/
 እናመስግነው/፪/ እግዚአብሔርን
 ምስጉን ነው የተመሰገነ/፪/

ከዓለት ላይ ወሃ ፈልቆልን ጠጣን ይህን ታላቅ አምላክ ኑ እናመስገን ሕዝቦች ደስ ይበለን ሕይወታችን ድኗል ሰይጣን ጠላታችን አፍሮ ተመልሷ  ንሴብሖ/፪/ ለእግዚአብሔር/፪/
 ስቡሐ ዘተሰብሐ/፪/
 እናመስግነው/፪/ እግዚአብሔርን
 ምስጉን ነው የተመሰገነ/፪/

አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር ጉልበታችን ቢዝል ፈተናው ቢበዛ ኃይላችን ጌታ ነው የዓለሙ ቤዛ  ንሴብሖ/፪/ ለእግዚአብሔር/፪/
 ስቡሐ ዘተሰብሐ/፪/
 እናመስግነው/፪/ እግዚአብሔርን
 ምስጉን ነው የተመሰገነ/፪/